Saturday, 27 June 2015 09:27

የግጥም ጥግ

Written by 
Rate this item
(10 votes)

ችጋር
አላፊ፣ አግዳሚው - ወጪና ወራጁ
የሰልፍ ተክተልታይ - ወደ ‘ሚሻው ሂያጁ
ነውና ምሳሌው፡-
እሾህ ለአጣሪው -ወንጀል ለፈራጁ፡-
ምስለተሰንካዮች - የሚግበሰበሱ
እንደ ምንጭ ሲፈልቁ - እንደ ‘ኋ ሲፈሱ
ቀለብ ሰፋሪያቸው ከቶ ማነው እሱ?
ሸክሎች ተሰብስበው አፈር እየላሱ፡፡
አንድስ‘ንኳ
በመስቀል ውዥንብር - በቁርባን ቱማታ
በመሃይም ቦታ፡-
የባልቴቶች ጌታ፡-
በግዝት ቅብጥርጥር፡-
በፍታት ድንግርግር፡-
ሚስጥረ ሥላሴ፤
ግዕዝ ወቅዳሴ፡-
በሰንበቴ ጉርሻ፤
በሙት ዓመት ቁርሻ
ባለትልቅ ድርሻ፡-
ከበሮ አስደግፈው አነጣጥረው በልክ፤
ወረብ አስተማሯት ውሽማዬን ብልክ
በመቋሚያ ሽብርክ፤ ቅዳሴ የ’ንብርክ፡፡
በካሣሁን ወ/ዮሐንስ
ከአማርኛ የግጥም መድብል የተወሰደ

Read 3999 times