Saturday, 02 May 2015 12:10

የኦባማ ኢሜይል በአጭበርባሪዎች ተሰበረ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

 የዋይት ሃውስ ባለስልጣናት ለሳምንታት በየዕለቱ መክረዋል

   ለጊዜው ማንነታቸው በውል ያልታወቀ የኢንተርኔት አጭበርባሪዎች የፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማን ኢሜይል በህገ-ወጥ መንገድ ሰብረው በመግባት፣ መረጃዎችን ማግኘት እንደቻሉ መረጋገጡን ስካይ ኒውስ ባለፈው ሰኞ ዘገበ፡፡
የዋይትሃውስ የደህንነት ሃላፊዎች ቻይናውያን አልያም ሩስያውያን ሳይሆኑ ሲሉ የጠረጠሯቸው እነዚህ የኢንተርኔት አጭበርባሪዎች፣ የይለፍ ቁልፉን ሰብረው በመግባት ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ለሌሎች ሰዎችና ድርጅቶች የላኳቸውንና ከሌሎች የተላኩላቸውን የኢሜል መልእክቶች ማግኜት መቻላቸው ተረጋግጧል፡፡ድርጊቱ የተፈጸመው ከሳምንታት በፊት ቢሆንም፣ የዋይት ሃውስ ባለስልጣናት ጉዳዩን ሸፋፍነውት እንደቆዩ የጠቆመው ዘገባው፣የአጭበርባሪዎቹ ጉዳይ አሳሳቢ መሆኑን የሚያመለክተው ባለስልጣናቱ ላለፉት ሳምንታት በየዕለቱ እየተሰበሰቡ በጉዳዩ ዙሪያ ሲመክሩ መቆየታቸው ነው ብሏል ዘገባው፡
ሩስያውያን የኢንተርኔት አጭበርባሪዎች የኦባማን የኢሜል መልዕክቶች ለማግኘት የቻሉት፣ ባለፈው አመት በዋይት ሃውስ የሴኪውሪቲ ሲስተም ላይ በደረሰው ቀውስ ያገኙትን ክፍተት በመጠቀም ነው ተብሎ እንደሚገመት የገለጸው ዘገባው፣ ይሄም ሆኖ ግን አጭበርባሪዎቹ ከፍተኛ ጥበቃ የሚደረግለትን የኦባማ  የብላክቤሪ ስልክ መልዕክቶች ማግኘት እንዳልቻሉ አክሎ ገልጧል፡፡

Read 2947 times