የአይሁዶች አባባል
ሰው ሲያቅድ እግዚአብሔር ይስቃል፡፡
እናት፤ ልጅ ሳይናገር ይገባታል፡፡
ሃጢዓትን ሁለቴ ከፈፀምከው ወንጀል አይመስልም፡፡
ፍየልን ከፊት ለፊት፣ ፈረስን ከኋላ፣ ሞኝን በየትኛው በኩል አትጠጋቸው፡፡
ብልህነትህን በተግባር እንጂ በቃላት አታሳይ፡፡
ሻማ ለመግዛት ፀሃይን አትሽጥ፡፡
እግዚአብሔር ሸክምን ሲሰጥ ትከሻም አብሮ ይሰጣል፡፡
እግዚአብሔር ሁሉም ቦታ ሊሆን ስለማይችል እናቶችን ፈጠረ፡፡
ለጎረቤቱ የሚፀልይ ለራሱ ይደርስለታል፡፡
ልዕልት ማግኘት የምትሻ ከሆነ ራስህን ልዑል አድርግ፡፡
እግር የሌለው ሰው እስከማገኝ ድረስ ጫማ የለኝም ብዬ አዝን ነበር፡፡
በዓይንህ ያላየኸውን በአፍህ አትመስክር፡፡
ሳሙና ሰውነትን እንደሚያጥበው ሁሉ እንባም ነፍስን ያጥባል፡፡
አባት ለልጁ ሲሰጥ ሁለቱም ይስቃሉ፤ ልጅ ለአባቱ ሲሰጥ ሁለቱም ያለቅሳሉ፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል