Monday, 06 April 2015 09:06

የየአገሩ አባባል

Written by 
Rate this item
(9 votes)

ለጅል መድሃኒቱ ሞት ብቻ ነው፡፡
በፀሐይ እረስ፣ በዝናብ አንብብ፡፡
ያልተጠየከውን ምክር አትለግስ፡፡
አንዳንዴ መድኀኒቱ ከበሽታው ይከፋል፡፡
የጫማ ሰሪ ልጅ ሁልጊዜ በእግሩ ይሄዳል፡፡
ስጦታ የሚቀበል ነፃነቱን ይሸጣል፡፡
መንሾካሾክ ባለበት ሁሉ ውሸት አለ፡፡
ገንዘብ የሌለው ሰው ገበያ ውስጥ ጥድፍ ጥድፍ ይላል፡፡
አንዴ የሰረቀ ሁልጊዜ ሌባ ነው፡፡
ሆድ ሲሞላ ልብ ደስተኛ ይሆናል፡፡
ቁራ ካረባህ ዓይንህን ይጓጉጡታል፡፡
ማልዶ የተነሳ ያልደፈረሰ ውሃ ይጠጣል፡፡
ጥርጣሬ የዕውቀት ቁልፍ ነው፡፡
ፅጌረዳውን የፈለገ እሾሁን ማክበር አለበት፡፡
ዓይነስውር በራሰ በራ ይስቃል፡፡
እባብ ለመያዝ የጠላትህን እጅ ተጠቀም፡፡
ነፋስ ያመጣውን ነፋስ ይወስደዋል፡፡
ልብ ውስጥ ያለውን ምላስ ያወጣዋል፡፡
በወጣት ትከሻ ላይ አሮጌ ጭንቅላት መትከል አትችልም፡፡
ሰነፍ በግ ፀጉሩ የከበደው ይመስለዋል፡፡

Read 2717 times