Monday, 16 March 2015 09:34

“ጋዜጣው ራሱን እያሳደገ እዚህ መድረሱ ጥሩ ነው”

Written by 
Rate this item
(0 votes)

አቶ ደስታ አስፋው
(በኢህአዴግ ፅ/ቤት የህዝብና ውጭ
ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ)
         አዲስ አድማስ ጋዜጣ በቆየባቸው 15 ዓመታት ውስጥ ጠንካራም ደካማም ጎኖች እንዳሉት ታዝቤያለሁ፡፡ ከጠንካራ ጎኖቹ መካከል የተለያዩ ጉዳዮችን በተከታታይ በመረጃ መልክ ለህዝብ ማድረሱ ነው፡፡ ከዚያ ውጪ አልፎ አልፎ የሚዛናዊነት ችግሮች ይታዩበታል፡፡ አዲስ አድማስ አሁን የደረሰበትን ደረጃ አይቶ፣ ጥንካሬዎቹን አጠንክሮ ጉድለቶቹን አርሞ ከቀጠለ፣ለሃገራችን የዲሞክራሲ ስርአት ግንባታ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ሊያደርግ ይችላል የሚል እምነት አለኝ፡፡ በግሌ ቢያንስ በመሰረታዊ የሙያው መርሆች ይሰራሉ ከምላቸው ጋዜጦች ውስጥ አስገባዋለሁ፡፡ አዲስ አድማስ የሚዲያ ሥራ በባህሪው የሚያጋጥመውን ተግዳሮት ተወጥቶ በየጊዜው ራሱን እያሳደገ፣ እዚህ መድረሱ ጥሩ ነው፤ ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል፡፡ ትልቁ ነገር ግን፣ ለህዝቡ መረጃ ለማድረስ በሚደረገው ጥረት የጋዜጠኝነትን መርህ መለኪያ ማድረግ ነው፡፡ የተሰሩ ጥሩ ነገሮችንም መዘገብ አለባችሁ፡፡ ለወደፊትም ጋዜጣው ደካማ ጎኑን አርሞ ጠንካራ ጎኑን ይበልጥ አጠናክሮ መቀጠል አለበት፡፡ እንኳን ለ15ኛ አመታችሁ አደረሳችሁ ለማለት እወዳለሁ፡፡  

Read 1281 times