ስልጣን ከያዝን ቦኮ ሃራም በናይጀሪያ አይኖርም ብለዋል
በመጪው ወር በሚካሄደው የናይጀሪያ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ኦል ፕሮግሬሲቭስ ኮንግረስ የተባለውን የአገሪቱ ተቃዋሚ ፓርቲ በመወከል የሚወዳደሩት የፓርቲው መሪ ሙሃሙዱ ቡሃሪ፣ ፓርቲያቸው ስልጣን ቢይዝ ቦኮ ሃራም ከተባለው አሸባሪ ቡድን ጋር ሰላማዊ ድርድር እንደማያደርግ አስታወቁ፡፡ ጽንፈኛውን ቡድን ለማጥፋት ብቸኛው አማራጭ የሃይል ጥቃት መሰንዘር ነው ያሉት ቡሃሪ፤ በስልጣን ላይ ያለው የአገሪቱ መንግስት በቡድኑ ላይ የሚያሳየውን መለሳለስ ክፉኛ ነቅፈውታል፡፡
“ቦኮ ሃራም የሰላም ፍላጎት የሌለው የጥፋት ቡድን ነው፤የሰላም ፍላጎት ቢኖረው ኖሮ 13 ሺ ናይጀሪያውያንን አይገድልም ነበር” ያሉት የቀድሞው የአገሪቱ የጦር አዛዥ ሙሃሙዱ ቡሃሪ፣ ፓርቲያቸው በምርጫው አሸንፎ ስልጣን ከያዘ፣ ቦኮ ሃራም በናይጀሪያ ግዛት ውስጥ ስንዝር መሬት እንደማይኖረው አስታውቀዋል፡፡
በሌላ በኩል የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ጉድላክ ጆናታን መንግስት፣ ሰሞኑን በአሸባሪ ቡድኑ ላይ የተጠናከረ ዘመቻ ማወጁን ያስታወቀ ሲሆን የተቃዋሚ ፓርቲው መሪ ግን “ፍሬ ቢስ” ሲሉ አጣጥለውታል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል