Saturday, 14 February 2015 16:00

ግብጽ በ36 ዜጎቿ ላይ የጣለችውን የሞት ፍርድ አነሳች

Written by 
Rate this item
(3 votes)

ግብጽ ከሁለት አመታት በፊት በሚናያ ግዛት በሚገኝ የፖሊስ ማዘዣ ጣቢያ ላይ ጥቃት ፈጽመዋል በሚል ባለፈው ሰኔ ወር የሞት ፍርድ ከጣለችባቸው 183 የሙስሊም ብራዘር ሁድ አባላት መካከል፣ የሰላሳ ስድስቱን የሞት ቅጣት ማንሳቷንና የፍርድ ሂደቱ እንደገና እንዲታይ ባለፈው ረዕቡ መወሰኑን ቢቢሲ ዘገበ፡፡ ፍርድ ቤቱ ሞሃመድ ባዲ የተባሉትን መንፈሳዊ መሪ ጨምሮ በ36 ተከሳሾች ላይ ጥሎት የነበረውን የሞት ቅጣት ለማንሳትና ፍርዱ እንደገና እንዲታይ የወሰነበትን ምክንያት በግልጽ አለማስታወቁን ዘገባው አመልክቷል፡፡
የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን ጨምሮ በርካታ አለማቀፍ ተቋማት በ183 የሙስሊም ብራዘር ሁድ ደጋፊዎች ላይ ፍርድ ቤቱ የጣለውን የሞት ቅጣት በአጽንኦት ሲተቹት እንደነበርም አስታውሷል፡፡
የሞት ፍርዱ ከተጣለባቸው 183 ግብጻውያን መካከል 147 የሚሆኑት የፍርድ ሂደታቸው በሌሉበት ሲታይ መቆየቱንም ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡

Read 1608 times