Saturday, 13 December 2014 10:21

መድረክ በነገው ሰልፍ የሚጠቀምባቸውን መፈክሮች ይፋ አደረገ

Written by  አለማየሁ አንበሴ
Rate this item
(7 votes)

         የኢትዮጵያ ፌደራላዊ አንድነት (መድረክ) በነገው እለት በአዲስ አበባ ለሚያከናውነው ሰላማዊ ሰልፍ ያዘጋጃቸውን መፈክሮች ይፋ ያደረገ ሲሆን በግንቦቱ አገራዊ ምርጫ ጠንካራ ቅስቀሳ ሊያካሂዱ ይችላሉ የተባሉ አባሎቶቼ እየታሰሩብኝ ነው ብሏል፡፡ ለነገው የመድረክ የተቃውሞ ሰልፍ ወደ 37 የሚጠጉ መፈክሮች የተዘጋጁ ሲሆን አብዛኞቹ በግንቦት ወር የሚደረገው ሃገራዊ ምርጫ ላይ የሚያተኩሩ ናቸው፡፡
“የሃገራችን ችግሮች በነፃና ፍትሃዊ ምርጫ በሚገለፅ የህዝብ ውሳኔ እንጂ በኃይል እርምጃ አይፈቱም”፣ “በማስመሰያ ምርጫ በየአምስት አመቱ ህዝብን ማታለልና ሀብቱን ማባከን ይቁም”፣ “የማስመሰያ ምርጫ ለማካሄድ ለሚባክነው የሃገርና የህዝብ ሃብት ኢህአዴግ ተጠያቂ ነው”፣ “ገለልተኛ የምርጫ ቦርድ በፖለቲካ ፓርቲዎች ተሳትፎ ይቋቋም”፣ በመንግስት ሃብትና ንብረት ኢህአዴግ የሚያካሂደውን ህገ ወጥ የምርጫ ዘመቻ እናወግዛለን፡፡
” የሚሉት ይገኙበታል፡፡
መድረክ ስለ ህግ የበላይነት፣ ስለ ፍትሃዊ የሚዲ አጠቃቀም፣ ስለ መደራጀትና መሰብሰብ መብት፣ ስለ ማህበራዊ አገልግሎት ችግር የሚያትቱ መፈክሮችንም ያዘጋጀ ሲሆን ስለ ኑሮ ውድነት፣ ስለ ህገወጥ የመሬት ወረራ እንዲሁም የመንግስት በሃይማኖት ጣልቃ መግባትን የሚኮንኑ መፈክሮችንም እንዳዘጋጀ ታውቋል፡፡
በሌላ በኩል በኦሮሚያ፣ በትግራይና በደቡብ ክልል በተለያዩ ዞኖችና ወረዳዎች በቀጣዩ ምርጫ የነቃ ተሳትፎ ይኖራቸዋል ተብለው የተገመቱ አመራሮቹና አባሎቹ ለእስር እየተዳረጉበት መሆኑን መድረክ አስታውቋል፡፡

Read 2516 times