Saturday, 15 November 2014 10:58

በኢቦላ ላይ ህዝባዊ ውይይት ሊካሄድ ነው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ የዓለም ስጋት በሆነው ኢቦላ ላይ ያተኮረ ህዝባዊ ውይይት የፊታችን ረቡዕ በግዮን ሆቴል ይካሄዳል፡፡
 የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚና የኢትዮጵያ ጤና አጠባበቅ ማህበር በጋራ ባዘጋጁት በዚህ ህዝባዊ ወይይት ላይ የኢቦላ ቫይረስ ምንነትና የመተላለፊያ መንገዶቹ እንዲሁም ስርጭቱ፣ ምልክቶቹ፣ የመጋለጫ መንገዶችና የቁጥጥር ዘዴዎቹን አስመልክቶ የጤና ባለሙያዎች ገለፃ እንደሚያደርጉ ታውቋል፡፡
የምዕራብ አፍሪካ አገራትን በተለይ ላይቤሪያና ሴራሊዮንን ክፉኛ ያጠቃው የኢቦላ ቫይረስ ወደ አገራችን እንዳልገባ ያስታወቀው የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፤ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ  ላይ በሰዓት 1ሺ ሰዎችን መመርመር የሚያስችል ዘመናዊ መሣሪያ እንደተከተለና በድንበሮች አካባቢም ባለሙያዎች መድቦ ቁጥጥር እያደረገ መሆኑን መግለጹ ይታወሳል፡፡

Read 1433 times