Friday, 06 January 2012 08:27

የዓለም ስፖርት ዋና የገቢ ምንጭ የትኬት ሽያጭ ነው

Written by  ግሩም ሠይፉ
Rate this item
(0 votes)

ዓለም አቀፍ የስፖርት እንቅስቃሴ በሚቀጥሉት 4 ዓመታት በእድገት መቀጠሉ የማይቀር ቢሆንም የታላላቅ መድረኮች አዘጋጆች በውድድርና መዝናኛ መካከል ያለውን ድንበር መለየት እንደሚቸግራቸው በፕራይስዎተርሃውስ ኩፐርስ የተሰራ ሪፖርት አመለከተ፡፡ በሚቀጥሉት 4 ዓመታት ከዓለም ስፖርት እንቅስቃሴ የሚገኘው አጠቃላይ ገቢ 145.3 ቢሊዮን ዶላር እንደሚደርስ የገመተው ፕራይስዎተርስ ኩፐርስ የገቢውን ሲሶ ድርሻ የትኬት ሽያጭ እንደሚሸፍነው ገልፃል፡፡

በዓለም የስፖርት እንቅስቃሴ ዘንድሮ የተገኘው አጠቃላይ ገቢ 118.7 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን ከባለፈው አመት በ2 % ወርዷል፡፡ ከቲኬት ሽያጭ 39 ቢሊዮን ዶላር፤ ከሚዲያ መብት 26.9 ቢሊዮን፤ ከስፖንሰርሺፕ 35.1 ቢሊዮን እና ከተለያዩ ንግድ እንቅስቅሴዎች 17.5 ቢሊዮን ዶላር በዓለም ዙርያ ገቢ መደረጉን የገለፀው ፕራይስዎተርሃውስ ኩፐርስ በሚቀጥሉት ሶስት ዓመታት ገቢው በ10% እድገት እንደሚያሳይ አስታውቋል፡፡ከ2006 ጀምሮ በነበሩት አራት የውድድር ዘመናት ብራዚል ቻይና ሩስያና ህንድ በስፖርቱ ወጪ የሚያደርጉት ገንዘብ በ7.7% ማሳደጋቸውን  የገለፀው ሪፖርቱ የሰሜን አሜሪካ አህጉር ከአጠቃላይ ገቢው 41% ድርሻ በመያዝ 49.9 ቢሊዮን ዶላር ገቢ እንዳስመዘገበና አውሮፓ ፤ መካከለኛው ምስራቅና አፍሪካ በጋራ 42.8 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተከታታይ ደረጃ እንደወሰዱ አረጋግጧል፡፡

 

 

 

Read 2884 times Last modified on Friday, 06 January 2012 08:33