Saturday, 27 September 2014 09:39

‘ሼልሾክ’ የተሰኘ እጅግ አደገኛ የኮምፒውተር ቫይረስ መጥቷል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

            ከ500 ሚ. በላይ ኮምፒውተሮችን ሊያጠቃ ይችላል

           በአለም ዙሪያ የሚገኙ ከ500 ሚሊዮን በላይ ኮምፒውተሮችንና ሰርቨሮችን ሊያጠቃ እንደሚችል የተነገረለት ‘ሼልሾክ’ የተባለ እጅግ አደገኛ የኮምፒውተር ቫይረስ ከሰሞኑ እየተሰራጨ እንደሚገኝ ቢቢሲ ዘገበ፡፡ የኮምፒውተር ባለሙያዎችን ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ ይህ አዲስ አይነት አደገኛ ቫይረስ ባሽ ተብሎ በሚጠራውና በበርካታ የሌኑክስና ማክ ኦፕሬቲንግ ሲስተሞች ውስጥ በሚገኘው የሶፍትዌር አካል ላይ ላይ ተሰራጭቶ Yተገኘ ሲሆን፣ ማንኛውንም አይነት ሲስተም በርቀት ሆኖ ለመቆጣጠር የሚያስችል ነው፡፡

በሱሬይ ዩኒቨርሲቲ የደህንነት ተመራማሪ የሆኑት ፕሮፌሰር አለን ውድዋርድ ለቢቢሲ እንደተናገሩት፣ አዲሱ ቫይረስ ባለፈው ሚያዝያ ወር ላይ ተከስቶ ከነበረው ኸርትብሊድ የተባለ ቫይረስ በእጅጉ የከፋ እና ማንኛውንም የኮምፒውተር ሲስተም ሊቆጣጠር የሚችል ነው፡፡የአሜሪካ የኮምፒውተር አደጋ ዝግጁነት ቡድን፣ ከሰሞኑ የተከሰተውንና በርካታ ድረ ገጾችን ሊያጠቃ እንደሚችል የተነገረለትን ይህን አደገኛ ቫይረስ በተመለከተ ለተጠቃሚዎች አፋጣኝ የማስጠንቀቂያ መልዕክት ያስተላለፈ ሲሆን፣ ከቫይረሱ ጥቃት ሊታደጋቸው የሚችለውን ተገቢ ጥንቃቄ እንዲያደርጉም መክሯል፡፡ የኢንተርኔት ወንጀለኞች ቫይረሱ የሚፈጥረውን ቀውስ በመጠቀም ኦፕሬቲንግ ሲስተሞችን ሊቆጣጠሩ፣ የሚስጥር መረጃዎችን ሊያገኙ፣ በመረጃዎቹ ላይ ለውጥ ሊፈጥሩና ሌሎች የወንጀል ድርጊቶችን ሊፈጽሙ እንደሚችሉም ባለሙያዎች ስጋታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ፡፡

Read 1800 times