Saturday, 20 September 2014 10:45

“ዓመቱ ለኢንቨስትመንት አመቺ ይሆናል የሚል ተስፋ አለኝ”

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

- ዶ/ር አረጋ ይርዳው (የሚድሮክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ)

       በኩባንያችን በኩል ባለፈው አመት የተከናወኑት ተግባራት በሙሉ አመርቂ ነበሩ፡፡ በተለይ በቴክኖሎጂ ግሩፑ አካባቢ ጥሩ ስራ ነው የተሠራው፡፡ በቀጣይ ደግሞ በተለይ የመብራት አገልግሎቱ መሻሻልና የባቡር ዝርጋታው መጠናቀቅ፣ በሀገራችን ያለውን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ መልካም ያደርጉታል የሚል እምነት አለኝ፡፡ በአጠቃላይ 2007 እና ከዚያ በኋላ ያለው ዘመን ለኢንቨስትመንቱ አመቺ ይሆናል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ቴክኖሎጂ ግሩፑን በተመለከተ የወርቅ ምርት የመሳሰሉትን ሥራዎች እያስፋፋን ነው፡፡ የምናስፋፋበትም ምክንያት እስከዚያ መብራቱም ይደርሳል ብለን ስለምናስብ ነው፡፡ በአጠቃላይ በአገራችን የሚታየው ነገር ተስፋ ሰጪ ነው፡፡ በተረፈ ለኢትዮጵያ ህዝብ ዘመኑ የሰላም፣ የጤናና የብልጽግና እንዲሆን እመኛለሁ፡፡

Read 1371 times