Print this page
Saturday, 30 August 2014 10:41

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አመቱን ክብረ ወሰን በያዘ ስኬት ማጠናቀቁን አስታወቀ

Written by 
Rate this item
(13 votes)

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለአለማችን የአቪየሽን ኢንዱስትሪ ፈታኝ የነበረውን የበጀት አመት ክብረ ወሰን ባስመዘገበ ስኬት ማጠናቀቁን አስታወቀ፡፡
አየር መንገዱ ከትናንት በስቲያ በፌስቡክ ድረገጹ ላይ ባስነበበው መረጃ እንዳለው፣ አመታዊ ገቢውን አምና ከነበረበት 21 በመቶ በማሳደግ፣ በአመቱ 46 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር አድርሷል፡፡ ተሳፋሪዎችን የማመላለስ አቅሙን በ17 በመቶ ከፍ ማድረጉንና ከተሳፋሪዎች የሚያገኘውን ገቢ በ16 በመቶ ማሳደጉንም አስታውቋል፡፡
እጅግ ዘመናዊ እንደሆነ የሚነገርለትን ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አውሮፕላን ጨምሮ፣ 13 አዳዲስ አውሮፕላኖችን ገዝቶ ወደ አገር ውስጥ ማስገባቱን የገለጸው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ 9 አዳዲስ መዳረሻዎች በረራ መጀመሩንም ተናግሯል፡፡

Read 3260 times
Administrator

Latest from Administrator