Saturday, 02 August 2014 10:51

አዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ 861 ሚ.ብር ማትረፉን ገለፀ

Written by  አለማየሁ አንበሴ
Rate this item
(0 votes)

   አዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ ባለፈው የበጀት ዓመት ከብድር ወለድ፣ ከተለያዩ አገልግሎቶች፣ ከኮሚሽንና ከአገልግሎት ክፍያ በጠቅላላው 1.9 ቢሊዮን ብር ገቢ አግኝቶ፣ 816 ሚሊዮን ብር ማትረፉን ገለፀ፡፡ የባንኩ ተቀማጭ ገንዘብም አምና ከነበረው 13.1 ሚሊዮን ብር ወደ 16.1 ሚሊዮን ብር ከፍ ማለቱ ተጠቁሟል፡፡ ከሐምሌ 2005 እስከ ሰኔ 2006 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ ባንኩ ካለፈው ተመሳሳይ ዓመት ጋር ሲነፃፀር በገቢም ሆነ በትርፍ የ35 በመቶ ጭማሪ ማስመዝገቡን በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡ በበጀት ዓመቱ ባንኩ በአዲስ አበባና በተለያዩ የክልል ከተሞች 35 አዳዲስ ቅርንጫቾችን የከፈተ ሲሆን በአሁን ሰዓት በመላ ሃገሪቱ በጠቅላላው 150 ቅርንጫፎችን በመክፈት ከግል ባንኮች ቀዳሚውን ስፍራ እንደያዘ አስታውቋል፡፡

አዲስ አበባን ጨምሮ በዋና ዋና ከተሞች የባንኩን ደንበኞች የ24 ሰዓት ኤቲኤም አገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግም 100 ተጨማሪ ኤቲኤም ማሽኖች አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርጓል፤ 400 አዳዲስ የክፍያ መፈፀሚያ ማሽኖችም በሱፐር ማርኬት፣ በሆቴሎች፣ በሲኒማ ቤቶችና በተለያዩ የመዝናኛ ስፍራዎች እንደተተከሉ የባንኩ መግለጫ ጠቁሟል፡፡ ባንኩ በተገባደደው የበጀት ዓመት ለአንድ ሺህ አንድ መቶ ሰላሳ ሁለት (1132) ዜጎች የሥራ እድል የፈጠረ ሲሆን በጠቅላላው የሰራተኞቹን ቁጥር ወደ አራት ሺህ ሰባት መቶ ሰማኒያ ሰባት (4787) ለማድረስ እንደቻለም ታውቋል፡፡

Read 1350 times