Saturday, 07 June 2014 14:23

የግጥም ጥግ

Written by 
Rate this item
(6 votes)

ዛሬስ ስሌቱ ስንት ሆነ?

“መሬት፣ሴትና ሀገር…፣ አንድ ናቸው”
አትበሉኝ፤ አንድነታቸው ከሩቅ ይቀፋል፣
ሶስቱም ባንድ ላይ የከሸፉ እንደሁ፣ ነገረ
ትምህርት ባፉ ይደፋል…!
የ‘ውነት፣ የ‘ውቀት ሀቲታችን፣ እንደ
ፈርስ እጣቢ ይከረፋል፤
ሰብአዊነት እስከ መለኪያው፣ በየጎሰኛው
ከርስ ሰጥሞ ይነጥፋል፤
በዘመን እርከን ሳይገደብ፣ ትውልድም
በትውልዱ ይጣፋል!
ታዲያ እኛ እንኳ፣ እናስላው ጎበዝ
የአዙሪት ርዕዮትዓለሙን  ጣጣ፣
‹‹የዜሮ ድምር ፖለቲካችን››፣ ዛሬም
‹‹ነጋቲቭ›› እንዳይመጣ…!
        መስከረም፣ 1998ዓ.ም.

Read 3423 times