ዛሬስ ስሌቱ ስንት ሆነ?
“መሬት፣ሴትና ሀገር…፣ አንድ ናቸው”
አትበሉኝ፤ አንድነታቸው ከሩቅ ይቀፋል፣
ሶስቱም ባንድ ላይ የከሸፉ እንደሁ፣ ነገረ
ትምህርት ባፉ ይደፋል…!
የ‘ውነት፣ የ‘ውቀት ሀቲታችን፣ እንደ
ፈርስ እጣቢ ይከረፋል፤
ሰብአዊነት እስከ መለኪያው፣ በየጎሰኛው
ከርስ ሰጥሞ ይነጥፋል፤
በዘመን እርከን ሳይገደብ፣ ትውልድም
በትውልዱ ይጣፋል!
ታዲያ እኛ እንኳ፣ እናስላው ጎበዝ
የአዙሪት ርዕዮትዓለሙን ጣጣ፣
‹‹የዜሮ ድምር ፖለቲካችን››፣ ዛሬም
‹‹ነጋቲቭ›› እንዳይመጣ…!
መስከረም፣ 1998ዓ.ም.
Published in
የግጥም ጥግ