Saturday, 07 June 2014 14:20

“ሤራ አታ ኾንሶ” እና “ኮንሶን ለህፃናት” ለንባብ በቁ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በአብዱል ፈታህ አብደላህ አዘጋጅነት በኮንሶ የባህል ህግ ላይ ጥናት ተደርጐበት የተዘጋጀው “ሤራ አታ ኾንሶ” የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ በቃ፡፡ መጽሐፉ ትኩረት ያደረገው በኮንሶ የባህል ህግ ስርዓት ላይ ሲሆን በጥናቱ ውስጥ የኮንሶ የአገር ሽማግሌዎችና የአካባቢው ተወላጅ ምሁራን ተሳትፈውበታል፡፡ በ197 ገፆች የተዘጋጀው መጽሐፉ፤ በኮንሶ የባህል ህግ ስርዓት ላይ ትኩረት ቢያደርግም አጠቃላይ የማህበረሰቡን ባህል፣ ወግ፣ ቋንቋና ሃይማኖታዊ ሁነቶች ይቃኛል፡፡ መጽሐፉ በኢትዮጵያ የፍትህ ሥርዓቶች ማዕከልና በኮንሶ ወረዳ አስተዳደር ትብብር ታትሞ በነፃ ለአንባቢያን ደርሷል፡፡ በተያያዘ ዜና የቱሪዝምና እና የሙዚየም ማውጫዎችን በማሳተም የሚታወቀው ሀገሬ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን፤ የኮንሶ ህፃናት ስለ አካባቢያቸው የቱሪዝም መስህቦች እንዲያውቁ የሚረዳቸውን “ኮንሶን ለህፃናት” የተሰኘ የቱሪዝም መጽሐፍ ለንባብ ያበቃ ሲሆን “ሴራ አታ ኾንሶ” ከተባለው መጽሐፍ ጋር በኮንሶ ካራት ከተማ ባለፈው ሳምንት ተመርቋል፡፡

Read 1340 times