Saturday, 07 June 2014 13:45

“አምሬፍ ኢትዮጵያ” ስያሜውን ቀየረ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በእናቶችና ህፃናት ጤና፣ በተላላፊ በሽታዎች፣ በንፁህ የመጠጥ ውሃ፣ በህክምናና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ በስፋት በመንቀሳቀስ የሚታወቀው አምሬፍ ኢትዮጵያ (Amref Health Africa በሚል ስያሜውን መቀየሩንና አዲስ አበባን ጨምሮ በአማራ፣ በአፋር፣ በኦሮሚያና በደቡብ ክልል ሥራውን በስፋት እንደሚያከናውን አስታወቀ፡፡
የድርጅተ ካንትሪ ዳይሬክተር ዶ/ር ፍሎሬንስ ቲሙ ሰሞኑን ለጋዜጠኞች በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተናገሩት፤ ድርጅቱ በእናቶችና ህፃናት ጤና፣ በንፁህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና በአቅም ግንባታ ሥራዎች ላይ በስፋት ይንቀሳቀሳል፡፡
የድርጅቱ ዓመታዊ በጀት ከ100 ሚሊዮን ዶላር በላይ እንደሆነ የጠቆሙት ዶክተሯ፤ ከዚህ ውስጥ 7 በመቶ የሚሆነው ድርጅቱ በአገሪቱ ለሚያከናውናቸው የጤናና የልማት ተግባራት እንደሚውል ተናግረዋል፡፡
እ.ኤ.አ በ1998 ተመዝግቦ በኢትዮጵያ ሥራ የጀመረው አምሬፍ ኢትዮጵያ ሰሞኑን ስያሜውን ወደ አምሬፍ ኸልዝ አፍሪካ  በመቀየር ሥራውን በስፋት መቀጠሉን ተናግረዋል፡፡

Read 1850 times