Saturday, 31 May 2014 14:17

ለ14ኛው ታላቁ ሩጫ ምዝገባ ሰኞ ይጀመራል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ለ14ኛው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የፊታችን ሰኞ ምዝገባው ሊጀመር ነው፡፡ ከስድስት ወር በኋላ   በአዲስ አበባ በሚካሄደው የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫው  ላይ ተሳታፊዎች 40ሺ  እንደሚሆኑ ይጠበቃል፡፡
የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አዘጋጆች እንዳስታወቁት ለ14ኛው የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ውድድር ሰኞ እለት በተመረጡ ስምንት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ መስርያ ቤቶች ምዝገባው የሚጀመር ሲሆን  ለመጀመርያዎቹ 1ሺ ተመዝጋቢዎች የልምምድ ቲሸርት እንደሚሰጥ ገልፀዋል፡፡
በሌላ በኩል በነገው እለት ከሚደረገው የቀለበት መንገድ የዱላ ቅብብል ጋር ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ያዘጋጃቸው ውድድሮች ብዛት 100 ደርሰዋል፡፡

Read 1525 times