Saturday, 31 May 2014 14:03

ህፃናት ለእግዚአብሔር የፃፏቸው ደብዳቤዎች

Written by 
Rate this item
(9 votes)

ውድ እግዚአብሔር -
ባቢ ቢራ ጠጥቶ ሲመጣ አልወድም፡፡ አፉ መጥፎ መጥፎ ይሸታል፡፡ በዚያ ላይ ይጮህብኛል። አንተ ነህ ቢራ የፈጠርከው? ለምን?
ሳሚ - የ6 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር -
እሁድ እለት ሙሽሮቹ  ቤተክርስትያን ውስጥ ሲሳሳሙ አየኋቸው፡፡ ፈቅደህላቸው ነው?
ሮዝ - የ5 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር -
ካንተ የተሻለ ለእግዚአብሔርነት የሚሆን ያለ አይመስለኝም፡፡ እንዲህ ያልኩት እግዚአብሔር ስለሆንክ አይደለም፡፡ የእውነቴን ነው፡፡
ቻርልስ - የ7 ዓመት ህፃን  
ውድ እግዚአብሔር -
ዳይኖሰርን ባታጠፋው ኖሮ መኖር አንችልም  ነበር፡፡ ትክክል ነው ያደረግኸው፡፡  
ኤርሚ - የ7 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር -
በዓለም ላይ ያሉትን ሰዎች በሙሉ መውደድህ በጣም ያስደንቃል፡፡ እኛ ቤት አራት ሰዎች ብቻ ናቸው ያሉት፡፡ ሁሉንም መውደድ ግን አልቻልኩም፡፡
ናኒ - የ8 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር -
ሌሊት ሌሊት አስፈሪ ህልሞች አያለሁ። ከእነማሚ ጋር ልተኛ ስል አድገሃል ተባልኩ። አስፈሪ ህልሞች ከየት ነው የሚመጡት? ይሄ የሚመለከተው ሰይጣንን ነው አይደል?
ሔኖክ - የ6 ዓመት ህፃን

Read 2817 times