Saturday, 31 May 2014 12:27

ተማሪዋ አስተማሪውን በጩቤ ወጋች

Written by 
Rate this item
(30 votes)

በአዲስ አበባ ገርጂ አካባቢ በሚገኘው የኢትዮ ፓረንትስ ት/ቤት የ11ኛ ክፍል ተማሪ የሆነችው ታዳጊ፤ የት/ቤቱን ዩኒት ሊደር አቶ ወንደሰን ተሾመን ሦስት ቦታ በጩቤ በመውጋት ተጠርጥራ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ስትውል፣ ተጐጂው በኮርያ ሆስፒታል በህክምና ላይ እንደሚገኙ ምንጮች ጠቆሙ፡፡ ለት/ቤቱ አዲስ ነች የተባለችው ተማሪ ትናንት ከጠዋቱ 5፡30 ላይ ወደ ዩኒት ሊደሩ ቢሮ ለቤተሰብ ስልክ ደውልልኝ በማለት ከገባች በኋላ አደጋውን እንዳደረሰች ታውቋል፡፡ ተማሪዋ አስተማሪውን ለምን በጩቤ እንደወጋች እስካሁን አልታወቀም።
አደጋው የደረሰባቸው የት/ቤቱ ዩኒት ሊደር አቶ ወንድወሰን ተሾመ፤ ከመምህርነታቸው በተጨማሪ፣ የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ እንደሆኑ ታውቋል።

Read 6786 times