Saturday, 31 May 2014 12:22

ህብረት ባንክ ባለ 32 ፎቅ ህንፃ ሊገነባ ነው

Written by 
Rate this item
(4 votes)

ህብረት ባንክ ለሚያስገነባው ባለ 32 ፎቅ ህንፃ፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ንግድ ስራ ኮሌጅ ፊት ለፊት በሚገኝ ቦታ ላይ የመሰረት ድንጋይ ተጣለ፡፡
የባንኩን ዘመናዊ ህንፃ ዲዛይን ለማድረግ ከ40 በላይ የኪነ-ህንፃ ባለሙያዎች የተወዳደሩ ሲሆን ህንፃው ባለ 4 ደርዝ የምድር ውስጥ የመኪና ማቆሚያ እንደሚኖረው ተገልጿል፡፡
ከትናንት በስቲያ የመሰረት ድንጋይ የመጣል ስነ-ስርአት ላይ ንግግር ያደረጉት የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ ታዬ ዲበኩሉ፤ ባንኩ ከእለት ወደ እለት በሁሉም ረገድ እያደገ መምጣቱን ጠቅሰው፤ የራሱን ዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ማስገንባቱ በህብረተሰቡ ዘንድ የገነባውን መልካም ስምና ዝና ወደ ላቀ ደረጃ እንዲያሸጋግር ያግዘዋል ብለዋል፡፡
በስነ-ስርአቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኘው አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ በበኩሉ፤ ባንኩ በግሉ ሴክተር የተሰማሩ ባለሀብቶችን በመደገፍ ከሚያደርገው ዘርፈ ብዙ ጥረት ጎን ለጎን አቅሙን በከፍተኛ ሁኔታ እያሳደገ መሆኑን ጠቁሞ፣ ህንፃው መገንባቱ የሚጠበቅና አስፈላጊም ጭምር ነው ብሏል፡፡  

Read 3996 times