ባርሴሎና ለሊዮኔል ሜሲ ሰሞኑን በሰጠው አዲስ የኮንትራት ውል ተጨዋቹን የዓለማችን ውዱ ተከፋይ አድርጎታል፡፡ እስከ 2018 በኑካምፕ ለማቆየት በፈጸመው ስምምነት በየዓመቱ 16.3 ሚሊዮን ፓውንድ ይከፍለዋል፡፡ 20 ሚሊዮን ዩሮ ወይም 27 ሚሊዮን ዶላር ወይም 580 ሚሊዮን ብር ማለት ነው፡፡ በዓለም ዋንጫ ሰሞን 27 ዓመቱን የሚደፍነው ሜሲ ባለፉት 11 ዓመታት ከባርሴሎና ጋር ለ8ኛ ጊዜ የኮንትራት ውል እና ማራዘሚያዎች መፈራረሙ ነው፡፡
የባርሴሎና የምንግዜም ከፍተኛ አግቢ ሲሆን በ425 ጨዋታዎች 354 ጎሎችን አግብቷል፡፡ 6 የላሊጋ፤ 3 የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ፤ 2 የኮፓ ዴላሬይ እና ሌሎች በድምሩ 21 ዋንጫዎችን አግኝቷል፡፡
በአጠቃላይ ዓመታዊ ገቢ እስከ 73 ሚሊዮን ዶላር የሚያገኘው ክርስትያኖ ሮናልዶ ይበልጠዋል፡፡ የሜሲ 65 ሚሊዮን ዶላር ነው፡፡
ለሊዮኔል ሜሲ እስከ 250 ሚሊዮን ፓውንድ የዝውውር ሂሳብ ይጠራል፡፡
Published in
ስፖርት አድማስ