Print this page
Saturday, 24 May 2014 15:13

የግጥም ጥግ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

የዕድገት 10ቱ ቃላት!
አንዱ የዕድገት ትርጉሙ ጠፍቶበታል
አንዳንዱ ቁልቁል ማደግም ዕድገት ነው ይላል!
አንዳንዱ እንኳን ማደግ ከነመወለዱም ጠፍቶበታል!
አንዳንዱ እንዴት እንደሚታደግ ማወቅ ተስኖታል!
አንዳንዱ ፎቅ ይሰራ ይሰራና የሚከራይ ሲያጣ፤ “ይህ ህዝብ ዕድገት አይገባውም” ይላል፡፡
አንዳንዱ ፎቅ ሰርቶ ሰርቶ ሰርቶ ጫፍ ይወጣና “መሬት ማለት ምን ማለት ነው?” ብሎ ይጠይቃል፡፡
አንዳንዱ “ዕድገት አለ ግን ወረቀት ላይ ነው ያለው፡፡ ስለዚህ ዋናው የወረቀት ዋጋ ማደግ ነው” ይላል፡፡
“አንዳንዱ ዕድገት ማለት ሌሎች ሲያድጉ ማየት ነው፡፡ ስለዚህ የድንኳን ሰባሪ እድገት ነው”! ይላል
አንዳንዱ እድገት ማለት ከዚህ ወዲያም ለምን እንዳላደግን ማሰብ ነው፡፡ በቃ ካሰብክ የግድህን ታድጋለህ” ይላል፡፡
አንዳንዱ ግን ጥብስቅ አድርጎ… አድጎ… አድጎ ከአቅሙ በላይ ተመንድጎ ማደጉን ማቆሙ ጨንቆት “ብቻዬን አድጌ እስከመቼ! የሚያግዘኝ ይቅር የሚቃወመኝ እንዴት ይጥፋ?
የኔን ፎቅ ማየት ካልቻለ
ጎጆው ሲፈረስ ይማር የለ?”
በቃ ዛሬ ገና ይግባው
ቦታ ቀይሮ ሲሰፍር ለውጥም ዕድገትም የሱው ነው፡፡
ግንቦት 2006 ዓ.ም (ለአፍቃሬ ዕድገቶች)

Read 3294 times
Administrator

Latest from Administrator