የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ለመጀመሪያ ጊዜ የእያንዳንዱን ክልል የጋብቻ ስነ - ስርዓትና ትውፊታዊ ክንውን ሰንዶ ሊያስቀምጥ እንደሆነ አስታወቀ፡፡ በዚህም መሰረት ሰኔ 2 ቀን 2006 ዓ.ም እያንዳንዱ ክልል፣ ክልሉን ይወክላሉ ያላቸውን የጋብቻ ሥርዓቶች ይዞ በመቅረብ ለሌላው ህብረተሰብ ያስተዋውቃል ተብሏል፡፡ የጋብቻ ስነ ስርዓቱና ትውፊታዊ ክንውኑ በመገናኛ ብዙሃን የሚሰራጭ ሲሆን ከዚያም በብሔራዊ ቴአትር ተሰንዶ ይቀመጣል ተብሏል፡፡ በዚህ ዝግጅት ላይ ሁሉም ክልሎች ተወክለው ይገኛሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር በላከው መግለጫ አስታውቋል።
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና