በሽመልስ ይፍሩ (ጤርጢዮስ ከቫቲካን) የተዘጋጀው “የተመለሱና ያልተመለሱ ጥያቄዎቼ” የተሰኘው መፅሃፍ ታትሞ እየተሸጠ ነው፡፡
መጽሃፉ፤ አንዱን ቅዱስ መጽሐፍ እያነበቡ በተለያየ ስም የተጠሩበትንና የተለያየ አቋም የያዙበትን ዐብይ ምክንያት እንደሚፈትሽ የገለፀው አዘጋጁ፤ ርዕሰ ጉዳዩም ስለ እግዚአብሔር፣ ስለ ሰውና ስለ ክርስቶስ ባላቸው የእምነት ግንዛቤ ላይ ብቻ የሚያተኩር ነው ብሏል፡፡
በመፅሃፉ ውስጥ የኦርቶዶክስ፣ የካቶሊክ፣ የፕሮቴስታንት፣ የሐዋርያዊት (በተለምዶ Only Jesus የሚባሉቱ) ቤተክርስቲያናት እና የይሖዋ ምስክሮች አገልጋዮች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ መጽሐፉ በ50 ብር እየተሸጠ ሲሆን በጃፋር የመጽሀፍት መደብር እየተከፋፈለ ይገኛል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና