የተለያዩ የቢዝነስ፣ የሞቲቬሽን እና መሰል መፅሀፍት በማዘጋጀት የሚታወቁት ዶ/ር አቡሽ አያሌው፤ ያዘጋጁት “ካይዘን” የተሰኘ መፅሀፍ በትላንትናው እለት በግራንድ ዮርዳኖስ ሆቴል ተመርቋል፡፡ ሩቅ ምስራቃዊያን ሳይንሳዊ እውነታውን ቀድመው በመረዳት ካይዘንን ተለውጠውበታል የሚሉት ዶ/ር አቡሽ፤ ሀገራችንም ካይዘንን ተግባራዊ ካላደረገች ያሰበችው ለውጥ ላይ እንደማትደርስ በማሰብ፣ የካይዘንን ግንዛቤ በህብረተሰቡ ውስጥ ለማስረፅ እንደተዘጋጀ ተናግረዋል በመፅሀፉ ምረቃ ላይ የተለያዩ እንግዶች የተገኙ ሲሆን በመፅሀፉ ዙሪያም ውይይት ተካሂዷል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና