በአሜሪካ
በፍቺ የሚጠናቀቁ ጋብቻዎች የሚቆዩበት አማካይ ጊዜ 8 ዓመት ነው፡፡
ሰዎች ፍቺ ከፈፀሙ በኋላ እንደገና ለማግባት በአማካይ ለሶስት ዓመት ይጠብቃሉ፡፡
ጥንዶች የመጀመሪያ ፍቺያቸውን የሚፈጽሙበት አማካይ ዕድሜ 30 ዓመት ነው፡፡
ወላጆቻችሁ ስኬታማ ትዳር የነበራቸው ከሆነ ለፍቺ የመጋለጥ ዕድላችሁ በ14 በመቶ ይቀንሳል
ከጋብቻ በፊት አብሮ መኖር የፍቺን ዕድል 40 በመቶ ይጨምራል፡፡
ኮሌጅ የተማራችሁ ከሆናችሁ፣ ለፍቺ የመጋለጥ ዕድላችሁ 13 በመቶ ይቀንሳል፡፡
ከአሜሪካ ህፃናት ገሚሱ የወላጆቻቸው ትዳር ሲፈርስ ይመለከታሉ፡፡ ከእነዚሁ ህፃናት ግማሽ ያህሉ የወላጆቻቸው ሁለተኛ ጋብቻ ሲፈርስም ያያሉ፡፡
ኦክላሆማ ከፍተኛ ፍቺ የሚፈፀምባት ግዛት ስትሆን ከግዛቷ ያገቡ አዋቂዎች መካከል 32 በመቶው ፍቺ ፈጽመዋል፡፡
ዛሬ በአሜሪካ ካሉ ህፃናት ውስጥ 43 በመቶው ያለአባት ነው የሚያድጉት፡፡
Published in
ጥበብ