Saturday, 22 March 2014 13:00

የአማርኛ ፊልሞች በኢቴቪ 3 እየታዩ ነው

Written by 
Rate this item
(8 votes)

“የሎሚ ሽታ” ፊልም ፕሮዱዩሰር የሆነው ማቭሪክ ፕሮሞሽን፤ ከኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ጋር በመሆን በኢቴቪ 3 “ማቭሪክ ፊልሞች የኢትዮጵያ” የተሰኘ የአማርኛ ፊልሞች ብቻ የሚታዩበት ፕሮግራም ጀመረ፡፡
“ፊደል አዳኝ” በሚለው ፊልም ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ የጀመረው ፕሮግራሙ፤ በየሳምንቱ ቅዳሜ ከ4፡30 እስከ 6፡30 የሚተላለፍ ሲሆን ሰኞ በተመሳሳይ ሰዓት በድጋሚ ይቀርባል፡፡ የማቭሪክ ፕሮሞሽን ማኔጂንግ ዳይሬክተር ፌቨን ታደሰ ለአዲስ አድማስ እንደገለፁት፤ ከዚህ ቀደም የውጭ ሃገር ፊልሞች የሚታዩበትን “ታላቁ ፊልም”ን መነሻ ያደረገው ፕሮግራማቸው፤ በሦስት ወር ጊዜ ውስጥ 10 ያህል የአማርኛ ፊልሞችን ካቀረበ በኋላ ባለሙያዎች በሚሰጡት የግምገማ ውጤት መሰረት አሸናፊው ፊልም ይሸለማል። በፕሮግራሙ የሚቀርቡ ሁሉም ፊልሞች፣ የሲኒማ ቤት የዕይታ ጊዜያቸውን ጨርሰው የወረዱ እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 5930 times