Tuesday, 04 March 2014 11:37

“አላቲኖስ” የአድዋ ድልን 120ኛ ዓመት በዓል በጣይቱ ሆቴል ያከብራል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

አላቲኖስ ፊልም ሰራዎች ማህበር ከኤድሚክ ፊልምና ቲያትር ካምፓኒ ጋር በመሆን የአድዋ ድልን 120ኛ ዓመት ክብረ በዓል “የዓድዋ ስነ-ጥበብ” በሚል መሪ ቃል በነገው ዕለት ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ በጣይቱ ጃዝ አምባ እንደሚያከብር አስታወቀ፡፡ ማህበሩ ለአዲስ አድማስ በላከው መግለጫ እንደጠቆመው፤ የአድዋን ሥነ-ጥበባዊነት የሚያጎሉ ጥናታዊ ዲስኩሮች በፊልም፣ በቲያትር፣ በሙዚቃ፣ በሥነ-ፅሁፍና ፍልስፍና ምሁራን አማካይነት ይቀርባሉ፡፡ ታዋቂ አርቲስቶችም አድዋን የሚያጎሉ ኪነጥበባዊ ትርዒቶች እንደሚያቀርቡ ተገልጿል፡፡ የአድዋ ጀግኖች እና አርበኞች ታሪክ በአርአያነት ለትውልድ እንዲሻገር ይዘከራሉ ብሏል- የአላቲኖስ መግለጫ፡፡

Read 1207 times