Print this page
Saturday, 22 February 2014 13:19

ወግ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

“አንድ ደራሲ በመግቢያው ስለ ጠቅላላ መፅሀፉ ይዘት ሲያብራራ ታላቅ ድግስ አዘጋጅቶ መግቢያ በሩ ላይ በመቆም ውስጥ ስለተዘጋጀው ምግብ ጣፋጭነት እየመሰከረ ወደ ብፌው አቅጣጫ እንደሚመራ ጋባዥ መሆኑ ነው፡፡
ደራሲውም ሆነ ጋባዡ መግቢያው ላይ ቆመው በአንድ አይነት ዜማ ታዳሚው ስለ ድግሱ በቂ ግንዛቤ ኖሮት እንዲገባ በማስረዳት ይደክማሉ፡፡ ይሄን ድግስ ለማዘጋጀት ስለ ተደከመው ድካም፣ በውጤቱም ስለተዘጋጁት አይነቶችም ያብራራሉ።
በውስጥ ስለተደገሰው ድግስ በራፍ ላይ ሆኖ የማብራራት አስፈላጊነት ወይም አላማ የታዳሚውን የመብላት ፍላጎት ማናር /አፒታይዘር/ ጭምር ሳይሆን አይቀርም፡፡ በእኔ እምነት ይህ ተግባር ተጋባዡን ጉጉ ያደርገዋል፡፡
በዚህ መፅሃፍ ውስጥ ስለተካተቱት ታሪኮች ይዘት ማውራት ካለብኝ ከአትኩሮታቸው በመነሳት እጀምራለሁ፡፡ በአንድ የማህበረሰብ ስብስብ ውስጥ (ሀገር ሊሆን ይችላል) ወሳኝ ሚና ስላላቸው፣ የየነዋሪውም ዋነኛ ግዱ ስለሆኑት ማለትም … ሀይማኖት፣ ፖለቲካና ማህበረ-ባህላዊ እሳቤ ለመዳሰስ ሞክሬያለሁ፡፡”  
ርዕስ - ሕዝብ እና ነፃነት
ደራሲ - ሚካኤል ዲኖ
ዋጋ - 44 ብር

Read 2967 times
Administrator

Latest from Administrator