Monday, 03 February 2014 13:48

የስፖርት ጋዜጠኛው አስቸኳይ ድጋፍ ይፈልጋል

Written by 
Rate this item
(5 votes)

የኢትዮጵያ ሬድዮ እና ቴሌቪዥን የስፖርት ጋዜጠኛ የሆነው መኳንንት በርሄ ላጋጠመው የደም መርጋት ህመም በደቡብ አፍሪካ ህክምናውን እየጀመረ ነው፡፡ ከትናንት በስቲያ የደም ናሙና የሰጠው የስፖርት ጋዜጠኛው፤ በትናንትናው እለት ደግሞ የዶፕለር ምርመራ አድርጎ በቀኝ እግሩ ላይ የደም ማመላለሻ ቧንቧ‹‹ ቬን›› መዘጋቱ ተረጋግጧል። ከሁለቱ ምርመራዎች ውጤት በኋላ የተዘጋውን የደም ማመላለሻ ቧንቧ የሚከፍትበትን ልዩ ህክምና በአስቸኳይ ማድረግ እንዳለበት በሃኪሞቹ ተነግሮታል፡፡ በደቡብ አፍሪካ የሚገኘው መኳንንት በርሄ ካጋጠመው የጤና እክል ሙሉ ለሙሉ ለመዳን ለሚያደርገው ከፍተኛ ህክምና ከ350 ሺ ብር በላይ ይጠበቅበታል፡፡ ለስፖርት ጋዜጠኛው ገንዘብ ማሰባሰብ ከተጀመረ አንድ ሳምንት ወዲህ ብዙም ባለመገኘቱ አሁንም ከፍተኛ ርብርብ ያስፈልጋል፡፡

ጓደኛው ትዕግስት ገመቹ በኢትዮጵያ ሬድዮ እና ቴሌቭዥን ድርጅት ሠራተኞች 43ሺ እንደተሰበሰበለት ገልፃ፤ አንዳንድ ድርጅቶች ድጋፍ ለመስጠት ቃል በገቡት መሰረት እየተጠባበቅን ነው ብላ፤ በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ገንዘቡ በሙሉ ተሰብስቦለት ህክምናው ቶሎ እንደሚጨርስ ተስፋ አደርጋለሁ ብላለች፡፡ ለህክምና የሚያስፈልገውን ገቢ ለማሰባሰብ የትእግስት ገመቹን አድራሻ ለምን መጠቀም እንዳስፈለገ ያስረዳቸው ጓደኛው ትእግስት ገመቹ፤ መኳንንት በአገር ውስጥ ስለሌለ ገንዘቡን እንዳስፈለገ ለማንቀሳቀስና ለመላክ እንዲቻል በመታሰቡ ነው ብላለች፡፡ በደቡብ አፍሪካ ሲካሄድ በቆየው የ3ኛው ቻን ቻምፒዮንሺፕ የኢትዮጵያን የምድብ 3 ጨዋታዎች በቀጥታ ስርጭት በማስተላለፍ እና የተለያዩ ዘገባዎችን በመስራት ለሙያው ያለውን ፍቅር እና ትጋት አሳይቷል፡፡ ዘገባውን በቀጥታ እየሰራ የነበረው መኳንንት በርሄ ነው ህክምናውን ለማድረግ እዛው ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅድስተ ማርያም ቅርንጫፍ የባንክ ቁጥር….. 1000070999076 ወይንም ተጨማሪ መረጃ ካስፈለገ ደግሞ ጓደኛውን ትዕግስት ገመቹን ማነጋገር ይቻላል፡፡ ስልክ…0910-10-17-93

Read 3912 times