Tuesday, 21 January 2014 10:22

ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ከፓርቲ ፖለቲካ ራሣቸውን አገለሉ

Written by  አለማየሁ አንበሴ
Rate this item
(11 votes)

ከአንድነት ፓርቲ በአመለካከት ልዩነት ለቀዋል

        የኢፌዴሪ ኘሬዚዳንት፤ ኋላም የተቃዋሚው አንድነት ለፍትህ እና ለዴሞክራሲ ፓርቲ ሊቀመንበር የነበሩት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ፤ ከእንግዲህ የፓርቲ ፖለቲካ በቃኝ በማለት አንድነትን ጨምሮ ከማንኛውም ፓርቲ ራሣቸውን እንግዳገለሉ ለአዲስ አድማስ ገለጹ፡፡ ዶ/ር ነጋሶ ራሣቸውን ከፓርቲ ፖለቲካ ያገለሉት በጤና መታወክ እና በእድሜ መግፋት ምክንያት መሆኑን ገልፀው፤ በቀጣይ በሀገሪቱ ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ አስተያየቶችንና ገንቢ ትችቶችን በመስጠት ብቻ ተወስነው እንደሚቆዩ አስታውቀዋል፡፡ በቅርቡ አንድነት ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ በኢ/ር ግዛው ሽፈራው የተተኩት ዶ/ር ነጋሶ፤ ባለፈው ዓመት ሚያዚያ ወር ላይ አንድነት መድረክን ከመገምገሙ ጋር በተያያዘ በተፈጠሩ የሃሣብና እና በአጠቃላይ የአመለካከትና የአቅጣጫ ልዩነቶች ከአንድነት ለመልቀቅ መገደዳቸውን ለአዲስ አድማስ ገልጸዋል፡፡ ዶ/ር ነጋሶ ራሣቸውን ከፓርቲ ፖለቲካ ቢያገለግሉም በአገሪቱ ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ግን በግል መሳተፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል፡፡

Read 3240 times