የሞት ምድብ በተባለው ምድብ 3 ከሱዳን፤ ኬንያ እና ማላዊ ጋር የተደለደለው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በመጀመርያ ጨዋታው ከሱዳን ጋር 1 እኩል አቻ የተለያየ ሲሆን በሳምንቱ አጋማሽ ላይ በኬንያ ሁለት ለባዶ ተሸንፏል፡
በሌላ በኩል ዘንድሮ ለ3 ተከታታይ አመት የሴካፋ ዞን ሻምፒዮናን ስፖንሰር ያደረገው ሰርኔጂቲ ብሬዌሪስ የተባለው የምስራቅ አፍሪካ ትልቁ ቢራ ጠማቂ ኩባንያ በ2014 በብራዚል በሚደረገው 20ው አለም ዋንጫ የሴካፋ ዞን በአንድ ብሄራዊ ቡድን እንዲወከል ድጋፍ እያደረገ ነው፡፡ ሰረንጄቲ ብሬወሪስ 35 ውን ሴካፋ ታስከር ሲኒዬር ቻሌንጅ ካፕ ስፖንሰር ያደረገው 450 ህ ዶላር በመለገስ ነው፡፡ የሴካፋ ምክር ቤት የዞኑን እግር ኳስ ለማሳደግ አባል አገራትና ስፖንሰሮች በታዳጊና ወታቶች ውድድሮች ላይ በቂ ትኩረትና ድጋፍ እንዲኖራቸው ያሳሰበ ሲሆን በቀጣይ አመት የዞኑን ውድድር ኬንያ እንድታዘጋጅ ወስኗል፡፡