Saturday, 18 January 2014 11:58

የ“ኢትዮጵያ ታሪክ-ከኢማም አህመድ እስከ ዐጤ ቴዎድሮስ” ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(5 votes)

በእርቅይሁን በላይነህ የተዘጋጀው “የኢትዮጵያ ታሪክ - ከኢማም አሕመድ እስከ አጤ ቴዎድሮስ” የተሰኘ የታሪክ መፅሃፍ ሰሞኑን ለንባብ በቃ፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ፣ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም የታሪክ ተመራማሪ ዶ/ር ተፈሪ መኮንን በመፅሃፉ ጀርባ ላይ በሰጡት አስተያየት፤ “ይህ መፅሃፍ በታሪክ ተመራማሪዎች ብዙም ትኩረት ያልተሰጠውን፣ ነገር ግን ምናልባትም ወሳኝ የሆነውን የኢትዮጵያን ታሪክ በአማርኛ ቋንቋ ስለሚዳስስ፣ ለአብዛኛው ኢትዮጵያዊ አንባቢ ተመራጭ እንዲሁም ወደፊት ለሚደረጉ የታሪክ ምርምሮች በመነሻነት የሚኖረው ድርሻ ከፍተኛ ነው” ብለዋል፡፡ በ364 ገፆች የተቀነበበው መፅሃፉ፤ ስድስት ምዕራፎች ያሉት ሲሆን በ79.99 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡

Read 4268 times