Saturday, 11 January 2014 12:24

ሆራቡላ የሥነጽሑፍ ዝግጅቱን ሰኞ ያቀርባል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በደብረዘይት (ቢሾፍቱ) ከተማና አካባቢዋ የሥነጽሑፍ አፍቃሪያን የተቋቋመው “ሆራቡላ ሥነጽሑፍ ማሕበር” 20ኛ የስነጽሑፍ ዝግጅቱን የፊታችን ሰኞ ከቀኑ 7፡30 በከተማው ሕይወት ሲኒማ ትንሿ አዳራሽ እንደሚያቀርብ አስታወቀ፡፡ “የብዕር አዝመራ” በሚል ርእስ በሚቀርበው ዝግጅት፤ የማሕበሩ አባላት የግጥም፣ መነባንብ፣ ጭውውት እና ሌሎች ኪነጥበባዊ ሥራዎቻቸውን ያቀርባሉ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ዝነኛው የፊልም ተዋናይ ግሩም ኤርምያስ፤የህይወትና የሙያ ተመክሮውን ለማህበሩ አባላት እንደሚያካፍል ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 1851 times