The secret በተሰኘው የመጀመሪያ መጽሐፏ ከፍተኛ ዝናን የተቀዳጀችው አውስትራሊያዊ ደራሲ ርሆንዳ ባይርኔ The hero በሚል ያወጣችው ሦስተኛ መጽሐፏ “ጀግና” ተብሎ ወደ አማርኛ ተተረጐመ፡፡ መጽሐፉን የተረጐመው ብርሃኑ በላቸው ነው፡፡ “እያንዳንዳችን ወደዚህች ምድር የመጣነው በየራሳችን መንገድ ራሳችንንና ዓለምን የማበልጸግ ዓላማ ይዘን ነው” የሚለው መጽሐፉ፤ “አንተም ልዩ ነህና ለስኬት ተዘጋጅ” ይላል፡፡ 182 ገፆች ያሉት መጽሐፉ፤ በ40.50 እየተሸጠ ነው፡፡