Friday, 03 January 2014 00:00

“የምሥራቅ ፈርጦች” ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በአሚር ዩኒስ ረሐስ የተፃፈው “የምሥራቅ ፈርጦች” የተሰኘ ታላላቅ የሐረሪ ተወላጆችን ታሪክ የያዘ መፅሃፍ ባለፈው ሳምንት ለንባብ በቅቷል፡፡ ስምንት የሚደርሱ የሐረሪ ሊቃውንቶችና የታሪክ ምሁራንን የሚያስተዋውቀው መፅሃፉ፤ መታሰቢያነቱን የሥነ ጽሑፍ ባለሙያ ለነበሩት ለአብዱል ሐፊዝ ከሊፋ መሐመድ እና ለመሐመድ ኢብራሒም ሱሌይማን አድርጓል፡፡
በመጽሐፉ ታሪካቸው ከተካተቱት መካከል የሳይንስ ሊቁ ፕሮፌሰር ዘኪ አብዱላሒ፣ የታሪክ ምሁሩ አህመድ ዘካሪያ፣ የሐረር የነፃነት አባት በሚል የተገለፁት ሼህ ኢብራሂም ጋቱርና ሌሎች ለሐረሪ ህዝብና ለኢትዮጵያ እድገት አስተዋጽኦ ያበረከቱ ግለሰቦች ይገኙበታል፡፡ ግለሰቦችም ትውልድ ሊማርበት የሚችል  አኩሪ ታሪክ አላቸው የሚለው ደራሲው፤ በመፅሃፉ ታላላቅ ሥራዎችን የሰሩና የታሪክ ባለውለታ የሆኑ የጥቂት ሐረሪዎችን ታሪክ ለመዳሰስ መሞከሩን በመግቢያው ላይ ገልጿል፡፡ በ413 ገፆች የተቀነበበው መፅሃፉ፤ በ80 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡
በሌላ በኩል በገጣሚ አለማየሁ ነጋ የተፃፉ ግጥሞችን ያካተተ ‹‹የተመዘዙ ሰበዞች›› የተሰኘ የግጥም መድበል ታትሞ ባለፈው ሳምንት  ለገበያ ቀርቧል፡፡ በ72 ገፆች ሰባ ሁለት ግጥሞችን የያዘው የግጥም መፅሐፍ በ30 ብር እየተሸጠ ነው፡፡

Read 2241 times Last modified on Monday, 06 January 2014 10:28