Saturday, 14 December 2013 11:50

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በህፃናት ሩጫው መሰረዝ ይቅርታ ጠየቀ

Written by  ግሩም ሠይፉ
Rate this item
(0 votes)

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የህፃናት ሩጫው በመሰረዙ በስፖርት ቤተሰቡ እና በህፃናት ላይ ለተፈጠረው መጉላላት ከፍተኛ ይቅርታ ጠየቀ። የህፃናት ሩጫውን ዘንድሮ ለ8ኛ ጊዜ ለማካሄድ ተደጋጋሚ ሙከራ ቢደረግም አልተቻለም፡፡ የውድድሩ አዘጋጆች በህፃናት ሩጫው እስከ 250 ተማሪ በማስመዝገብ ለመሳተፍ ከፍተኛ ፍላጎት የነበረውን ‹‹ፋውንቴን ኦፍ ኖውሌጅ›› ትምህርት ቤት ለማበረታት ዛሬ ልዩ የሩጫ ውድድር እንደተዘጋጀም ተናግረዋል፡፡ 3500 ህፃናትን በማሳተፍ ሊካሄድ ታስቦ የነበረው የህፃናት ሩጫው የአዲስ አበባ ፖሊስ ለልጆች ደህንነት ሲባል እንደሰረዘው ያስታወሱት የውድድሩ አዘጋጆች፤ ዋናው የ10 ኪሎሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ በተሳካ ሁኔታ ከተካሄደ ከሁለት ሳምንት በኋላ ለማድረግ የነበረው ጥረትም አልተሳካም ብለዋል፡፡ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በህፃናት ሩጫው ለመሳተፍ የተመዘገቡ ሁሉ የመሮጫ ቲሸርታቸውን በመያዝ በለገሃር ቴሌ፤ ቦሌ አካባቢ በሚገኘው የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ቢሮ እና በስታድዬም ዙርያ በሚገኘው ቴድ የስፖርት ትጥቅ መሸጫ ተገኝተው ሜዳልያቸውን መውሰድ እንደሚችሉ አስታውቋል፡፡

Read 1419 times Last modified on Saturday, 14 December 2013 11:56