Print this page
Saturday, 14 December 2013 11:41

የሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ የስፖርት አካዳሚ እያስገነባ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ የሚያስገነባው ሁለገብ የስፖርት አካዳሚ እና የመወዳደርያ ስፍራ 42 በመቶ መጠናቀቁ ተገለፀ፡፡ ከ530 ማሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚሆንበትን አካዳሚው የሚገነባው አፍሮፅዮን ኮንስትራክሽን ሲሆን አማካሪው ሺጌዝ ኮንሰልታንሲ ነው፡፡ ዩኒቨርሲቲው የዘንድሮውን የከፍተኛ ትምህርት የስፖርት ፌስቲቫል በዚሁ ሁለገብ የስፖርት አካዳሚና የመወዳደርያ ስፍራ እንደሚያስተናግድም ታውቋል፡፡ የስፖርት ፌስቲቫሉ ከመጀመሩ 10 ቀናት ቀናት ቀደም ብሎ የአካዳሚው የመጀመርያው የግንባታ ደረጃ ይጠናቀቃል፡፡ የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዓመታዊ የስፖርት ፌስቲቫል ከየካቲት 1 እስከ 16 ሲከናወን ድረስ 34 ዩኒቨርስቲዎች እና ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በ12 የስፖርት ዓይነቶች የሚካፈሉ ከ6 ሺ በላይ ስፖርተኞች በማሳተፍ ይወዳደሩበታል፡፡

የሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ በሁለገቡ የስፖርት አካዳሚና የመወዳደርያ ስፍራ እያስገነባቸው ካሉት የስፖርት መወዳደርያዎች መካከል ሶስትና ሁለት ውድድሮችን ማስተናገድ የሚችሉ አምስት የእጅና ቅርጫት ኳስ ሜዳዎችን ጨምሮ ሁለት የሜዳ ቴኒስ፣የዋና እና የእግር ኳስ ሜዳ ይገኙባቸዋል። ከእነዚህ 5 የስፖርት መወዳደርያ ሜዳዎች የሁለቱ ግንባታ ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቅ የቀሪዎቹ ደግሞ 85 በመቶ የግንባታ ስራው መጠናቀቁ ተገልጿል። በግንባታ ላይ ከሚገኙት የስፖርት መወዳዳርያዎች 25 ሺ ተመልካቾችን ማስተናገድ የሚችለው የእግር ኳስ ሜዳ እንዲሁም የሜዳ ቴኒስና የዋና መወዳደርያዎች የግንባታ ስራ 50 በመቶ የተከናወነ ሲሆን እስከ ጥር ወር መጨረሻ ሙሉ በሙሉ እንደሚጠናቀቁ ይጠበቃል፡፡ የሁለገብ የስፖርት አካዳሚና የመወዳደርያ ስፍራ ግንባታው በዩኒቨርሲቲው ለሚሰጠው የመጀመርያና ሁለተኛ ድግሪ የሰውነትና ጤና ማጎልመሻ ትምህርት አገልግሎት የሚውሉ 10 የመማርያ ህንጻዎችም ግንባታን ያካትታል፡፡

Read 1374 times
Administrator

Latest from Administrator