Saturday, 07 December 2013 12:38

29ኛው “ግጥም በጃዝ” ረቡዕ ይቀርባል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በወጣትና አንጋፋ ከያንያን በየወሩ የሚቀርበው “ግጥም በጃዝ” 29ኛ ዝግጅቱን የፊታችን ረቡዕ ከምሽቱ 11፡30 ጀምሮ በራስ ሆቴል አዳራሽ እንደሚያቀርብ አዘጋጆቹ ገለፁ፡፡ በምሽቱ የጥበብ ዝግጅት ላይ ገጣሚ ነቢይ መኮንን፣ ሰዓሊና ቀራጺ በቀለ መኮንን፣ አበባው መላኩ፣ ሜሮን ጌትነትና ገዛኸኝ ፀጋው ግጥም ሲያቀርቡ፤ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ወግ፣ በኃይሉ ገብረመድሕን ደግሞ ዲስኩር ያቀርባሉ ተብሏል፡፡ የዝግጅቱ መግቢያ በነፍስ ወከፍ 50 ብር ነው፡፡

Read 1718 times