Sunday, 24 November 2013 17:14

700ሚ. ብር የፈጀው ኢሊሌ ኢንተርናሽናል ሆቴል ዛሬ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(6 votes)

በአዲስ አበባ ከተማ ካዛንቺስ እምብርቱ ላይ ከአፍሪካ ኢኮኖሚክስ ኮሚሽን ፊት ለፊት በ700 ሚሊዮን ብር የተሠራው ባለ 5 ኮከብ ዘመናዊ ኢሊሌ ኢንተርናሽናል ሆቴል ዛሬ ይመረቃል፡፡
አቶ ገምሹ በየነ የተባሉ ባለሀብት ግዙፍ ኢንቨስትመንት የሆነው ባለ 10 ፎቅ መንትያ ሆቴል፤ 154 ክፍሎች ሲኖሩት የዘመኑ ቴክኖሎጂ ያፈራው መሳሪያ የተገጠሙለት መሆኑ ታውቋል፡፡
ኢሊሌ ኢንተርናሽናል ሆቴል፤ ሁለት ፕሬዚዴንሻል ክፍሎችና 16 ጁንየር ሱት፣ ስታንዳርድ፣ ኪንግ ሳይዝ፣ ደብል ትዊን፣ ፔንት ሃውስ ክፍሎች፣ አሉት፡፡ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ሬስቶራንትና ባር፣ የሕፃናት መጫወቻ፣ የወጣቶች የኦሎምፒክ ደረጃ መዋኛ፣ ስፓና ጂምናዚየም…አለው፡፡
ሆቴሉ 10ኛ ፎቅ ፕሬዚዴንሻል ሱት ላይ ሆነው በሁሉም አቅጣጫ ከተማዋን እየቃኙ ለመዝናናት ያመቻል፡፡ ቀልብን የሚስቡት የመኝታ ክፍሎቹ፤ መታጠቢያ ገንዳና ሻወር፣ ብሮድ ባንድ ኢንተርኔት፣ 42 ኢንች ቴሌቪዥን ሳተላይት ቲቪና ስልክ፣…አላቸው፡፡
ኢሊሌ ሆቴል ጥሪ የተደረገላቸው ከፍተኛ የመንግስት ባለሥልጣናት፣ ዲፕሎማቶች፣ ኢንቨስተሮች፣ የሃይማኖት አባቶችና፣ ታዋቂ ሰዎች በተገኙበት ዛሬ እኩለ ቀን ላይ በይፋ ተመርቆ አገልግሎት እንደሚጀምር ተገልጿል፡፡
ሆቴሉ፣ በአሁኑ ወቅት ለ300 ሠራተኞች የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፤ በሙሉ አቅሙ ሥራ ሲጀምር የሠራተኞቹ ቁጥር 450 እንደሚደርስ የሆቴሉ ባለቤት አቶ ገምሹ በየነ ገልፀዋል፡፡

Read 4520 times