Saturday, 31 August 2013 11:50

አቢሲኒያ ባንክ ከ351 ሚ.ብር በላይ አተረፍኩ አለ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

አቢሲኒያ ባንክ ዘንድሮ 351.2 ሚሊዮን ብር አጠቃላይ ትርፍ ማግኘቱንና ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ12.2 በመቶ ብልጫ እንዳለው ገለፀ፡፡ ባንኩ በላከው መግለጫ ላይ እንዳስታወቀው፤ የባንኩ አጠቃላይ ገቢ 895 ሚሊዮን ብር መድረሱንና ካለፈው ዓመት በ126 ሚሊዮን ብር ብልጫ ያለው መሆኑን ጠቁሟል፡፡ ለተለያዩ የንግድና አገልግሎት ዘርፎች በአጠቃላይ 4.7 ቢሊዮን ብር ብድር የሰጠ መሆኑን የገለፀው ባንኩ፤ አጠቃላይ ተቀማጭ ሂሣቡ 8.5 ቢሊዮን ብር መድረሱን አስታውቋል፡፡ አቢሲኒያ ባንክ 371ሺ 420 የሚሆኑ የገንዘብ አስቀማጭ ደንበኞች እንዳሉት መግለጫው ጠቅሶ፤ በተለያዩ የአገሪቱ ከተሞችና ክልሎች 82 የሚደርሱ ቅርንጫፎችን ከፍቶ ለደንበኞቹ አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኝ አመልክቷል፡፡

Read 14877 times