Saturday, 24 August 2013 11:10

“እዩና እመኑ” የመዝሙር ቪሲዲ ነገ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ጥንታዊውና ታሪካዊውን የአቡነ መልከፄዴቅ ገዳም ይበልጥ ለማስተዋወቅና ለቱሪስቶች ለማስጐብኘት እንዲሁም ለመርዳት በአርቲስቶች የተሰራው “እዩና እመኑ” ቪሲዲ ነገ በቅድስት ስላሴ ካቴድራል አዳራሽ ይመረቃል፡፡
ትዕግስት ግርማ፣ ይገረም ደጀኜ፣ መሰረት መብራቴና ሌሎች ታዋቂ አርቲስቶች የተሳተፉበት ቁጥር አንድ “እዩና እመኑ” ከዚህ በፊት ተመርቆ ለገበያ ከቀረበ በኋላ በተደረገው ገዳሙን የማስተዋወቅ ስራ እስካሁን የ13 አገራት አምባሳደሮች፣ ሀይሌ ገ/ስላሴና የጀርመኑ ፕሬዚዳንት የጐበኙት ሲሆን ዘወትር ቅዳሜ ከ33-40 መኪና ጐብኚዎች ወደ ስፍራው እንደሚጓዙ ተጠቁሟል።
በአቡነ መልከ ፄዴቅ ገዳም እጅግ አስገራሚ ከሆኑት መስህቦች መካከል የሰው ሬሳ ከአመታት በኋላ አለመበስበሱ፣ ያለቀለም መርገጫ በእጣን መዓዛ ብቻ የሚሰራ ማህተም፣ ከ800 ዓመት በላይ ዕድሜ ያለው ደወል እና ሌሎችም እንደሚገኙበት ይታወቃል፡፡

Read 1675 times