በጋዜጠኛና ደራሲ ቴዎድሮስ ሽፈራው የተዘጋጁ ስድስት የተረት መፃህፍት ሰሞኑን ለንባብ በቁ፡፡ “ባለማሩ ገላ ሰውዬ”፣ “ደግ ለራሱ”፣ “ደጓ ዳክዬ ”፡ “ሆዳሙ ዘንዶ”፣ “ቀብራራዋ ድመት” እና “ትንሿ ሻሼ” የተሰኙት መፃህፍት ህፃናትን እያዝናኑ የሚያስተምሩ ሲሆኑ የንባብ ልምድ በማዳበር ረገድም ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርጉ አዘጋጁ ተናግሯል፡፡ መፃህፍቱ እያንዳንዳቸው በ15.00 ለገበያ ቀርበዋል፡፡ ብር ጋዜጠኛና ደራሲ ቴዎድሮስ ሽፈራው፤ በኤፍ ኤም 96.3 የተለያዩ ፕሮግራሞችን የሚያዘጋጅ ሲሆን በተለይ “ቀይ መብራት” በሚለው ፕሮግራሙ ይታወቃል፡፡