Saturday, 20 July 2013 09:52

ገቢዎችና ጉምሩክ ከእቅዱ በላይ ታክስ መሰብሰቡን ገለፀ

Written by  መታሰቢያ ካሳዬ
Rate this item
(2 votes)

የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን በያዝነው ዓመት ከተለያዩ የታክስና የቀረጥ ምንጮች ከ84 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ለአዲስ አድማስ በላከው መረጃ አስታወቀ፡፡ ዘንድሮ የተሰበሰበው ገቢ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በ13.5 ቢሊዮን ብር እንደሚበልጥ ተገልጿል፡፡ ባለስልጣን መ/ቤቱ የላከው መረጃ እንደሚያመለክተው፤ በዘንድሮ ዓመት ከ2003 በጀት ዓመት ጀምሮ እስከ 2005 ዓ.ም ድረስ በሦስት አመታት ውስጥ 201 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ እቅድ ነበር፡፡

ከተለያዩ ታክሶችና የገቢ ምንጮች የተሰበሰበው ገንዘብ ግን ከእቅዱ በላይ 206 ቢ. ብር ገደማ እንደሆነ ባለስልጣኑ ገልጿል፡፡ በየአመቱ በሚሰበሰበው ታክስ ላይ ከፍተኛ ጭማሪ የሚታየው ግን በአዲስ አበባ ነው፡፡ ከአዲስ አበባ አስተዳደር ብቻ ታክስና ታክስ ካልሆኑ ገቢዎች እንዲሁም ከማዘጋጃ ቤት ገቢዎች ዘንድሮ 9.15 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ፣ 9.34 ቢሊዮን ብር መሰብሰቡን ገልጿል፡፡ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ4.18 ቢሊዮን ብር (የ81%) ጭማሪ ማሳየቱን መረጃው ያመለክታል፡፡

Read 13887 times