ገነት ንጋቱ የኪነጥበበ ፕሮሞሽን እና ፊልም ፕሮዳክሽን በደራሲና አዘጋጅ ገነት ንጋቱ የተሰራውን “ሐማርሻ” ፊልም እንደሚያስመርቅ አስታወቀ። ድርጊታዊ የሆነው የ95 ደቂቃ የቤተሰብ ፊልም ተሠርቶ እስኪጠናቀቅ አንድ ዓመት ወስዷል፡፡ ግንቦት 18 በአዲስ አበባ የግል ሲኒማ ቤቶች በማግስቱ ግንቦት 19 ከምሽቱ 11 ሰዓት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ትያትር በሚመረቀው ፊልም ላይ ገነት ንጋቱ፣ ተዘራ ለማ፣ ካሌብ አርአያስላሴ፣ ዘላለም ይታገሡ፣ ምስራቅ ታዬ እና ሌሎችም ተውነዋል፡፡