Saturday, 04 May 2013 12:15

አርቲስት ቻቺ ታደሠ ለአፍሪካ ህብረት በግል ኮንሰርት አዘጋጀች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የአፍሪካ ህብረት የተመሠረበትን 50ኛ አመት ምክንያት በማድረግ በቻቺ ኢንተርናሽል አርቲስት ማናጅመንት የተሰናዳ የአፍሪካ ሙዚቃ ፌስቲቫል ግንቦት 3 እና 4 በሚሊኒየም አዳራሽ ይቀርባል፡፡ በአርቲስት ቻቺ ታደሠ በሚመራው ዝግጅት ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሰባት የአፍሪካ ሃገራት የተውጣጡ ሙዚቀኞች ተሳታፊ እንደሚሆኑ አዘጋጆቹ በጋዜጣዊ መግለጫቸው አስታውቀዋል፡፡ አርቲስት ቻቺ ታደሰ፤ ዝግጅቱን እንዲያደምቁ የ40 አገራት አርቲስቶችን ለመጋበዝ ብትሞክርም በኤምባሲዎች ትብብር የተሳካው የስድስት ሀገራት መሆኑንና ሂደቱ አድካሚ እንደነበር አመልክታለች፡፡

በዝግጅቱ ላይ ከኢትዮጵያ ሃይሌ ሩትስ እና ቺጌ ባንድ እንዲሁም ቻቺ ራሷ “I am an African” የሚለውን ዘፈኗን በመዝፈን ተሣታፊ እንደሚሆኑ ይጠበቃል፡፡ ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚካሄደውን የሙዚቃ ዝግጅት ፌስቲቫል ለመታደም ከጠዋቱ 3-12 ሰዓት ለሚቀርበው ለአዋቂዎች 50 ብር፣ ለህፃናት በነፃ ሲሆን ለምሽት የሙዚቃ ዝግጅቶች ለአንድ ሰው መግቢያ የ200 ብር ቲኬት መዘጋጀቱን አስተባባሪዎቹ አስታውቀዋል፡፡

Read 2946 times