Saturday, 27 April 2013 11:51

የግጥም ጥግ

Written by 
Rate this item
(4 votes)

ገና ከጅምሩ
በቤት አራሥነት ሸክም … በአዲስ ኑሮ
አሐዱ ብዬ
የራስ ማስተዳደር ማተብ ሳጠልቅ … ከወላጅ እትብት
ተገንጥዬ
ሲሟሽ ሲሟሽ ሲታሰስ … ሲጋገር የመኖር እንጎቻዬ
በቆራስማ ማጥንት ታጥና … ማጠንሰስ ስትጀምር ገንቦዬ
ኑሮን አልፋ ብዬ ኑሮን በስመአብ ብዬ
ኑሮ ኪራራይሶን
ገና አንዲት ዶቃ ላማትብ ስቆጥር
ምነው ያደርገኛል እንደመፍዘዝ ነገር
እንደመቆናጠር
ተስፋን መቁረጥ አይሉት ወይ ተስፋን ማጠናከር
መበራታት አይሉት ወይ መደነጋገር
ብቻ የሆነ ስሜት ብቻ የሆነ ነገር
እኩል አይሉት ሠናይ ደስታ አይሉት ሥቃይ
ብቻ የሆነ ሥሜት ግልጽ ያልሆነ ጉዳይ

***

ሰሙ ዝቅ ወርቁ ርዝቅ
በቀመር ተሰልቶ፣
በዋጋ ተዋዝቶ፣
በሰም ቢታሸግም
ያለ ወርቅ እሺ አይልም፡፡
የዛሬ ጨረታ ኩሩ ነው ቀብራራ፤
ራሱን ይኮፍሳል፤
በታክቲክ ዝቅ ብሎ፣
በቴክኒክ ከፍ ይላል፡፡
(“ከጃርት ወደ ጃርት” ከሚለው
የካሣሁን ከበደ
የግጥሞች እና ወጐች መድበል የተወሰደ - 2000 ዓ.ም)

 

 

Read 4082 times Last modified on Saturday, 27 April 2013 12:01