Monday, 08 April 2013 09:56

በ2 ሚ. ብር የሶርያ ምግቦች ሬስቶራንት ተከፈተ

Written by 
Rate this item
(4 votes)

የሶርያ ምግቦች አዘጋጅቶ ለተጠቃሚዎች የሚያቀርብ ሬስቶራንት በ2 ሚሊዮን ብር ተቋቁሞ በአዲስ አበባ አገልግሎት መስጠት የጀመረ ሲሆን ሦስት ተጨማሪ ሬስቶራንቶችን ለመክፈት እንደተዘጋጀ ሶሪያዊው ባለሀብት ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያን ጨምሮ በግብጽ፣ ፊሊፒንስ፣ ዱባይ፣ ቤሩት እንዲሁም በሶሪያ ተመሣሣይ ሬስቶራንቶችን መክፈታቸውን የሚናገሩት የድርጅቱ ባለቤት አህመድ አሊ በክሪ፣ ሬስቶራንቱ የሶሪያ ባህላዊ ጣፋጭ መብሎችንም ሰርቶ በማቅረብ የሚያስተዋውቅ ነው ብለዋል፡፡

በሶሪያ ለምግብ የሚጠቀሙባቸው ግብአቶች ከኢትዮጵያ ጋር ተመሣሣይ እንደሆኑ ጠቁመው፤ ኢትዮጵያውያን የሶርያ ምግቦችን እንደሚወዷቸው እርግጠኛ ነኝ ብለዋል፡፡ “ሲሪያን ስዊት ኤንድ ሬስቶራንት” በተጨማሪ በአዲስ አበባ ለሚከፈቱ ሦስት ተመሣሣይ ሬስቶራንቶች ሠራተኞችን እያዘጋጀ ሲሆን፤ እስካሁን ለ12 ኢትዮጵያውያን ሼፎች የጣፋጭ ምግቦች አሠራር ስልጠና መሠጠቱን አህመድ በክረ ገልፀዋል፡፡ ከሬስቶራንት አገልግሎቱ በተጨማሪም በትላልቅ አለማቀፍ ስብሠባዎች የምግብ መስተንግዶ እንደሚያቀርቡ የተናገሩት ባለሀብት፣ አንድ የምግብ ኢንዱስትሪ ኩባንያን ለመግዛት በድርድር ላይ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡

Read 3644 times